ኢዲአር ከኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ጋር በትብብር መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡ ****
መስከረም 24 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢዲአር)፡- የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አ.ማ (ኢዲአር) ከኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ጋር በትብብር መስራት የሚስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡
ስምምነቱን የፈረሙት የኢዲአር ዋና ስራ አስፈፃሚ አብዲ ዘነበ (ዶ/ር) እና የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩብ ዋና ስራ አስፈፃሚ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ ናቸው፡፡
በስምምነቱ መሰረት ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ለባቡር መሠረተ ልማት ግብአት የሚሆኑ የተለያዩ የብረታ ብረት፣ ኤሌክትሪክና ኤሌክትሮኒክስ እንዲሁም የፕላስቲክ ምርቶችን እንደሚያቀርብ ተገልጿል፡፡
ስምምነቱ ተግባራዊ ሲሆን ኢዲአር የሚያጋጥሙትን የባቡር መሠረተ ልማት መለዋወጫ ዕቃዎች እጥረት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቅርፍ ተመላክቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ኢዲአር በከፍተኛ የውጪ ምንዛሬ ለመለዋወጫ ግዢ የሚያወጣውን የውጪ ምንዛሬ ማዳን ያስችላል ተብሏል፡፡
የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ኢንዱስትሪዎች የሆኑት አዲስ ማሽንና መለዋወጫ ማምረቻ ኢንዱስትሪ፣አቃቂ ቤዚክ ሜታልስ ማምረቻ ኢንዱስትሪ፣ብረታ ብረት ፋብሪኬሽን ኢንዱስትሪ፣የፓወር ኢኩመንትስ ማምረቻ ኢንዱስትሪና የኢትዮጵያ ፕላስቲክ ኢንዱስትሪዎች እነዚህን የባቡር መሠረተ ልማት መለዋወጫ ዕቃዎች እንደሚያመርቱ የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ ገልፀዋል፡፡
ኢዲአር እየሰጠ የሚገኘውን የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት በባቡር መሠረተ ልማት መለዋወጫ እጥረት ምክንያት ክፍተት እንዳይፈጠር ለማድረግ ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የሚያቀርበው የተለያዩ መለዋወጫዎች ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዲሚያበረክቱ የኢዲአር ዋና ስራ አስፈፃሚ አብዲ ዘነበ (ዶ/ር) ጠቁመዋል፡፡
በመግባቢያ ሰነዱ መሠረት በአስቸኳይ የጋራ የቴክኒክ ግብረ ሀይል በማቋቋምንና ዝርዝር ተግባራትን በመለየት ወደ ተግባር መግባት የሚያስችሉ ነጥቦችን ላይ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ተቋማቱ በጋራ የሚሯቸውን ስትራቴጂያዊ ስራዎች በፍጥነትና በጥልቀት ለይቶ በማቅረብ ወደ ስራ እንዲገባ ማድረግ እንደሚገባ ከስምምነት ተደርሷል፡፡
Facebook
Twitter
LinkedIn
Recent Posts
- Ethio-Djibouti Railway s.c. and the FDRE TVT Institute have signed an MOU.
- የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አ..ማ እና የኢፌድሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራፈሙ፤
- ኢዲአር በ2016 በጀት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት በወጪ ገቢ እንቅስቃሴ ያስመዘገበውን የ12.3 በመቶ ድርሻ ለማሳደግ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ተገለፀ፤
- Ethio Djibouti Rail Transport reported revenue of 998.13 million birr in the first quarter of fiscal 2016, according to CEO Abdi Zenabe (DR).
- The delegation led by Saudi Arabia’s Minister of Transport and Logistics visited Mojo Dry Port and Endode Railway Cargo Station.